Post

ተቀበል …

ተቀበል …

By Admin

ተቀበል …

አፋፉ ላይ ቆሜ … ሳየው አሻግሬ
ሰብሮ ሲከምረው … የመሰለኝ አውሬ
ስጠጋው ለየሁት … አወይ መታወሬ
ለካስ ሰውየው ኖሯል … የሚሉት “አጅሬ”

ተቀበል …

ድንገት ሳይታሰብ … ብልጭ! ያለ ‘ለታ
ከጉም ደመናው ኣፍ … ተመዞ ሲወጣ
እንደ ደረቅ እንጨት … ሰንጥቆ ‘ሚጥለው
ፋኖ መብረቅ እንጂ … ማን ነው ‘ሰው’ የሚለው?
ያን የእሳት ፍላፃ … ስጋ የሚያለብሰው?

ተቀበል …

ንቆ ቁጭ ቢል … ፍርሃት መስሏቸው
ሲወዛወዙ … ምድር ጠቧቸው
ደግሞ ተነሳ … ሊያስቀምጣቸው
ከደጅ ጉድጓዱ … ሊወዝፋቸው

ተቀበል …

ያልበላውን ሲያክ … በጥፍር ጥርሱ
ለያዥ ቸግሮ … ለገናዥ ቄሱ
መጣ ያ ፋኖ … ፎጣ ለባሹ
በልኩ ቀዶ … ከፈን አልባሹ

ተቀበል …

ለውብ ሳዱላ … ትላንት ተድሮ
ማልዶ ሸፈተ … ክላሻ አፍቅሮ፥
ድሮስ መች ለምዶ … መኝታ ከአልጋ
ተዉት ከሜዳው … ሲያጋድመው ይንጋ

ተቀበል …

ጀግና እና ጀበና  … መለየት አቅቶት
አለቀ የኣብይ ዘብ … ጎጃም ገብቶ አዳልጦት ፥
እንዳላ’ሳደረ … ከጎን ሆኖ ጥላ
ጎንደሬ ጉድጓድ ነው … ይውጣል ሲጣላ

ተቀበል …

መሬ ለጠላቱ … ወዳጅ ለወገኑ
መገን የኣማራ ልጅ … ዱር- ጫካ ድንኳኑ

 

*** (የቀለም ቃላቱን ስውር ፍቺ ለኣንባቢ ትቼዋለሁ)

Comments are closed.