ወቅታዊ ዕውነታዎችን ለማንበብ ዓይኔ በሳይበሩ ዓለም ከድህረ-ገጽ ወደ ድህረ-ገጽ ሲሯሯጥ፡ ድንገት በኣንድ ምስል ተደናቅፎ ወደቀ፦ መንግስት ለሀዘን መግለጫ ዝቅ ብለው እንዲውለበለቡ በሰቀላቸው ሶስት ባንዲራዎች። ዓይኔ’ን ከወደቀበት ትቶ፡ መንፈሴ – በታሪካችን ባንዲራችን እንዲህ ዝቅ ብሎ የተውለበለበበትን መሪር የሀዘን አጋጣሚም ለማስታወስ ወደኋላ ኮበለለ። ከንቱ ድካም ነበረ።
ሀሳቤ ከኋልዮሹ ጉዞ ሲመለስ፡ የዓይኔ እንቅፋት፣ የመገረሜን ምክንያት – ከላይ የምትመለከቱትን ፎቶ – በደንብ ማስተዋል ጀመርኩ። እናንተስ? አሰቃቀሉን ተመልክታችኋል? የእጥፋቱን ብዛት ታዘባችኋል? መስመሩ በዝቶ፣ አንዱ ባንዲራ ሰማንያ ቦታ ተሰባብሮ፣ ከአፍ እና ከአፍንጫ ጉድፍ ማፅጃ መሀረብ አንሶ፣ ተጠቅልሎ ስትመለከቱ፡ ሰቃ’ዮ ግለሰብ፡ ባንዲራውን ከሚስጢር ኪሱ አለበለዚያም ከገንዘብ ቦርሳው መዞ እንዳወጣው አልገመታችሁም?
ይገርማል፦ እንኳን የሀገር እና የህዝብ መለያ የሆነው ባንዲራ፡ የመንደር መሸታ ቤት አስተናጋጅ ዩኒፎርምም ክብር ኖሮት ይተኮሳል፣ ተስተካክሎ ይለበሳል። ባንዲራ እኮ የኣንድ ህዝብ መጠሪያ/መለያ ነው፤ ቃላታዊም ባይሆን ቀለማዊ ስም። ፎቶው አስገረመኝ እንጂ አላስቆጨኝም። ምክንያቱም፦ ትላንት “ጨርቅ” ነው ብለው ካረከሱት፡ ዛሬ ቢያጨማደዱት አይደለም ቢቦጫጭቁት ምን ያስቆጫል? ብቻ … ዝቅ ማለትዋ ቢያስከፋኝ … “ዝቅ እንዳደረጉሽ ዝቅ ይበሉ!” አልኩኝ፦
የዚህ ግጥም አብዛኛው ስንኝ እና ሐረግ ለአንባቢው ፍቺ ያስቸግራል የሚል ዕምነት ባይኖረኝም፤ ለግንዛቤ ያህል ግን አንዱን ቃል መፍታት እወዳለሁ፦
ግንባር = ዕድል (የማታሽን ግንባር = ጧሪ፣ ደጋፊ)
ቃል / May 2015.